የክልሉ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር ተስፋዬ ዴቢሶ የሜሪጆይ ኢትዮጲያ ሀዋሳ የኩላሊት እጥበት ማዕከልን ተዘዋውረው በጎበኙበት ወቅት እንደገለፁት ማዕከሉ የኩላሊት እጥበት ለሚያስፈልጋቸው አካላት እያከናወነ ያለው በጎ ተግባር እጅግ ከፍተኛ መሆኑን ገልፀው ሀሉም የህብረተተሰብ ክፍል የማዕከሉን በጎ ተግባር በመደገፍ የበኩሉን እንዲወጣ ሲሉ አፅንኦት ሰጥተው አሳስበዋል።
የክልሉ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ከተቋሙ አመራርና አባላት ጋር በመወያየት ማዕከሉን የመደገፍ ስራ እንደሚሰራ ተናግረዋል።



